Site Loader
Bole sub-city, Alfoz Plaza 5th floor office No. 504

2016 መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ / Annual General Assembly 2024

“የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች”  የ2016 ዓ.ም. በጀት አመት  6ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ!! መስከረም 05 ቀን 2017 ዓ.ም ድርጅቱ በ2016 ዓ.ም. የ6ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔው  ከ90% በላይ አባላቱ በተገኙበት ዝርዝር የማህበሩን ስራዎች በጥልቀትገምግሟል:: ከዚህም በመነሳት ድርጅቱ በቀጣይ ዓመታት ሊከተላቸው የሚገባቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጧል። ከዚህምበተጨማሪ ጉባኤው የድርጅቱን  የ2016 ዓ.ም. ኦዲት ሪፖርት  እንዲሁም የ2017 ዓ.ም የበጀት ዓመት የስራ እና የበጀት እቅዶች ላይ  በጥልቀት በመወያየት አስፈላጊውን ማሻሻያዎች በማድረግ አፅድቋል::   እንደዚሁም በድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት የሥራ ጊዜያቸዉን የጨረሱ የጠቅላላ ጉባኤ እና የስራ አመራር ቦርድ አባላትንአስመልክቶ ገሚሶቹ ለተጨማሪ አንድ የስራ ዘመን እንዲያገለግሉ፣ በተወሰኑት አመራር አባላት ምትክ ደግሞ አዳዲስ የአመራርአባላትን መርጧል። በመጨረሻም የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ አባል ለመሆን በቀረቡ አዳዲስ ማመልከቻዎች ላይ ተነጋግሮ ሁሉምአመልካቾች የድርጅቱ አባል ለመሆን ያቀረቡትን ማመልከቻዎች ተቀብሏል። የዚህ ዓመት ጉባዔ በአባላቱ መካከል የበለጠ ግንኙነትን እና ትብብርን ለመፍጠር በሚያስችል  መልኩ የማህበሩን አባላት ያሰባሰበሆኖ ነው ያለፈው። —————————— “Lawyers for Human Rights” held its 6th Regular…

በረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ላይ ከሰብዓዊ መብት የሲቪክ ድርጅቶች የቀረበ አስተያየት / Comments from human rights civic organizations on the draft transitional justice policy

ድርጅታችን ‘የህግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች’ በአገራችን ተግባራዊ ይደረጋል በሚል እንቅስቃሴ የተደረገበት ካለው  የሽግግርፍትህ ጋር በተያያዘ በፖሊሲ ሰነድ ዝግጅቱ ላይ በተናጠል እና ከሌሎች ሲቪል ማህበራት ጋር በጋራ በመሆን ምክረ ሃሳቦችንበማቅረብ በንቃት ሲሳተፍ የቆይ ከመሆኑም በላይ ለተግባራዊነቱም መደላደል የሚሆኑ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል። አሁንምየሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነዱ በቅርቡ ፀድቆ ስራ ላይ ሊውል እንደሆነ እየተነገረ ባለበት ደረጃ ድርጅታችን ከሌሎች ሲቪል ማህበራትጋር በጋራ በመሆን የፖሊሲ ሰነዱ ሊኖረው በሚገባው የመጨረሻ ይዘትና ቅርፅ ላይ አስተያየታችንን እንደሚከተለው አቅርበናል ———————- Our organization, Lawyers for Human Rights, has been actively engaged by itself and…