Site Loader
Bole sub-city, Alfoz Plaza 5th floor office No. 504

በረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ላይ ከሰብዓዊ መብት የሲቪክ ድርጅቶች የቀረበ አስተያየት / Comments from human rights civic organizations on the draft transitional justice policy

ድርጅታችን ‘የህግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች’ በአገራችን ተግባራዊ ይደረጋል በሚል እንቅስቃሴ የተደረገበት ካለው  የሽግግርፍትህ ጋር በተያያዘ በፖሊሲ ሰነድ ዝግጅቱ ላይ በተናጠል እና ከሌሎች ሲቪል ማህበራት ጋር በጋራ በመሆን ምክረ ሃሳቦችንበማቅረብ በንቃት ሲሳተፍ የቆይ ከመሆኑም በላይ ለተግባራዊነቱም መደላደል የሚሆኑ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል። አሁንምየሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነዱ በቅርቡ ፀድቆ ስራ ላይ ሊውል እንደሆነ እየተነገረ ባለበት ደረጃ ድርጅታችን ከሌሎች ሲቪል ማህበራትጋር በጋራ በመሆን የፖሊሲ ሰነዱ ሊኖረው በሚገባው የመጨረሻ ይዘትና ቅርፅ ላይ አስተያየታችንን እንደሚከተለው አቅርበናል ———————- Our organization, Lawyers for Human Rights, has been actively engaged by itself and…